የሀገር ውስጥ ዜና

ምክር ቤቱ የ28 ቢሊየን ብር ተጨማሪ በጀት አፀደቀ

By Tibebu Kebede

April 10, 2020

አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 2 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የ28 ቢሊየን ብር ተጨማሪ በጀት በሙሉ ድምጽ አጸደቀ።

ምክር ቤቱ ዛሬ ባካሄደው 2ኛ ልዩ ስብሰባው የ2012 በጀት ዓመት የፌደራል መንግስት የተጨማሪ በጀት እና የወጪ አሸፋፈን ማስተካከያ ረቂቅ አዋጅን መርምሮ በሙሉ ድምፅ አፅድቆታል።

ምክር ቤቱ ያፀደቀው የገቢ፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ያቀረቡትን የ28 ቢሊየን ብር ተጨማሪ በጀት የውሳኔ ሃሳብ መሆኑን የኢቢሲ ዘገባ ያመላክታል።

ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ! https://t.me/fanatelevision