Fana: At a Speed of Life!

በናይጀሪያ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ቦላ ቲኑቡ ማሸነፋቸው ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 22፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በሣምንቱ መጨረሻ በናይጄሪያ የተካሄደው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ የገዢው ፓርቲ ዕጩ ቦላ ቲኑቡ አሸናፊነት መጠናቀቁ ተገለጸ።

የሀገሪቷ ገለልተኛ የምርጫ አሥፈጻሚ ኮሚሽን እንዳስታወቀው፥ የቀድሞው የሌጎስ አስተዳዳሪ ቦላ ቲኑቡ 8 ነጥብ 79 ሚሊየን ድምፅ በማግኘት አሸናፊ ሆነዋል።

ዋና የቲኑቡ ተቀናቃኝ እና ተፎካካሪ የነበሩት አቲኩ አቡበከር ደግሞ 6 ነጥብ 98 ሚሊየን ድምፅ በማግኘት በጠባብ የድምፅ ልዩነት ፕሬዚዳንታዊ ምርጫውን ሳያሸንፉ መቅረታቸውን ሬውተርስ ዘግቧል፡፡

በናይጄሪያ ወጣቶች ዘንድ ተወዳጅ የሆኑት ፒተር ኦቢ 6 ነጥብ 1 ሚሊየን ድምጽ ማግኘታቸውም ነው የተገለጸው፡፡

ተቃዋሚ ፓርቲዎች በቴክኖሎጂ ታግዟል የተባለውን የምርጫ ሂደት እና ውጤት አንቀበልም ማለታቸውም ተዘግቧል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.