ሀገራዊ የታክስና የጉምሩክ ሕግ-ተገዢነት ንቅናቄ መክፈቻ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
የገቢዎች ሚኒስትር ዓይናለም ንጉሤ ÷ኢትዮጵያ በሁሉም መስክ ተከብራ እንድትቀጥል ግብር ከፋዮች ለሀገራቸው ታማኝ በመሆን አዲስ የአድዋ ድል ምዕራፍ መጻፍ እንደሚገባቸው ገልጸል፡፡
ዓድዋ ከኢትዮጵያም ባለፈ ለአፍሪካ ታላቅ የኩራት ምንጭ መሆኑን ጠቅሰው÷ቀደምት አያቶቻችን ኢትዮጵያን ከነክብሯ ለማቆየት ያሳዩትን አንድነት፣ ጀግንነትና ፅናት በመውረስ የአሁኑ ትውልድ ግብርን ለሀገር ክብር መክፈል ይኖርበታል ብለዋል።
በበጀት ዓመቱ ከ450 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ መታቀዱን እና ባለፉት ሰባት ወራት ከ258 ቢሊየን ብር በላይ መሰብሰቡን አንስተዋል፡፡
ኢትዮጵያ ካላት አቅም አንጻር የሚገባትን ገቢ ለመሰብሰብ የግብር ከፋዩ ታማኝነት፣ የአስፈጻሚ አካላት ቁርጠኝነትና ቀልጣፋ አሰራር ሊኖር ግድ ይላልም ነው ያሉት።
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-