Fana: At a Speed of Life!

ስድስተኛው ዙር የበጎ ፈቃደኛ ወጣቶች ስልጠና መጋቢት 4 ቀን ይጀመራል

አዲስ አበባ፣ የካቲት 28፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ስድስተኛው ዙር የበጎ ፈቃደኛ ወጣቶች ስልጠና መጋቢት 4 ቀን 2015 ዓ.ም እንደሚጀመር የሰላም ሚኒስቴር አስታወቀ።

የሰላም ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ታዬ ደንደአ ÷ በስልጠናው ከተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች የተውጣጡ ከ15 ሺህ በላይ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች እንደሚሳተፉ ገልጸዋል።

በጎ ፈቃደኞቹ ስልጠናቸውን ካጠናቀቁ በኋላ በተለያዩ የሀገሪቷ ክፍሎች በመሰማራት በተለያዩ ዘርፎች ነጻ አገልግሎት እንደሚሰጡ አመላክተዋል።

የበጎ ፈቃድ ስልጠናው ለአንድ ወር የሚቆይ ሲሆን÷ በስራ ፈጠራ፣ ስነ ልቦና እና ተጓዳኝ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ መሆኑም ተገልጿል።

ባህር ዳር፣ ጅማ፣ ዋቻሞ እና ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲዎች ስልጠናው የሚሰጥባቸው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መሆናቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.