ዶ/ር ዓለሙ ስሜ ከጅቡቲ ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ኦማር ጌሌ ጋር መከሩ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 28፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዶ/ር ዓለሙ ስሜ ከጅቡቲ ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ኦማር ጌሌ ጋር ተወያዩ ፡፡
በጅቡቲ የኢትዮጵያ አምባሳደር ብርሃኑ ፀጋዬ በትዊተር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ፥ የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትሩ ዶ/ር ዓለሙ ስሜ ለሥራ ጉብኝት ጅቡቲ መሆናቸው ይታወቃል፡፡
በዚህ የሥራ ጉብኝት ወቅትም ሚኒስትሩ ከሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ኦማር ጌሌ ጋር ተመካክረዋል።
ኢትዮጵያ እና ጅቡቲ በትራንስፖርት ዘርፍ በጋራ ሊሠሩ በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ እንደተወያዩም ነው የተገለጸው።
የዲኪል-ጋላፊ መንገድን ማጠናቀቅ እና ለተሸከርካሪዎች እንቅስቃሴ ምቹ ሁኔታን መፍጠርን አስመልክተውም ተወያይተዋል፡፡
በውይይቱ መነሣቱን በጅቡቲ የኢትዮጵያ አምባሳደር ብርሃኑ ፀጋዬ በትዊተር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት አስታውቀዋል።
#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!