የሀገር ውስጥ ዜና

በጅጅጋ ዩኒቨርሲቲ የኮሮና ቫይረስ መመርመሪያ ላብራቶሪ ማዕከል ተመረቀ

By Tibebu Kebede

April 11, 2020

አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 3 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በጅጅጋ ዩኒቨርሲቲ የኮሮና ቫይረስ መመርመሪያ ላብራቶሪ ማዕከል በሶማሌ ክልል ምክትል ርእሰ መስተዳደር አቶ ሙስጠፌ ሙሁመድ ተመረቀ።

በቫይረሱ የሚጠረጠሩ ግለሰቦች ናሙናን ወደ አዲስ አበባ በመላክ ምርመራ ይደረግ እንደነበር ያነሱት ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በዛሬው እለት ተመርቆ ስራ የጀመረው ማእከል ምርመራውን በክልሉ ለማድረግ የሚያስችል በመሆኑ ተናግረዋል።