የሀገር ውስጥ ዜና

የተለያዩ አካላት በአዲስ አበባ በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ለአደጋ ተጋላጭ ለሆኑ ነዋሪዎች ድጋፍ ማድረጋቸውን ቀጥለዋል

By Tibebu Kebede

April 12, 2020

አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 4 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ)  የተለያዩ አካላት በአዲስ አበባ በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ለአደጋ ተጋላጭ ለሆኑ ነዋሪዎች ድጋፍ ማድረጋቸውን ቀጥለዋል።

በዚህም መሰረት ዛሬ የተለያዩ አካላት ለከተማ አስስተዳድሩ  ድጋፉን አስረክበዋል።

  1. የካ ክፍለ ከተማ አርሶ አደሮች፡-100 ኩንታል ጤፍ 2. ንፋስ ስልክ ላፍቶ አርሶ አደሮች፡- ፡130 ኩንታል ጤፍ 3. አቃቂ ቃሊቲ አርሶ አደሮች፡- ፡-233 ኩንታል ጤፍ 4. ቶሪያ ሳሙና ፋብሪካ ፡-400 ካርቶን ሳሙና 5. ሃበሻ አስጎብኚ 1 ሃይሩፍ መኪና እና 300 ካርቶን ሳሙና 6. ኦሞቲክ ጀነራል ፒ. ኤል. ሲ 550 ኪሎግራም ሙዝ፣120 ኩንታል ድንች፣60 ሳጥን ቲማቲም ፣60 ሳጥን ሽንኩርት እና ሴፍቲ ጃኬት 500 እንዲሁም 1000 የፊት ማስክ 7. ኮማ አስመጪና ላኪ ከሰውነት ቢሻው አካዳሚ ጋር በመተባበር 70 ካርቶን የልብስ እና የገላ ሳሙና፣50 ኩንታል ጤፍ 8. ጂ እና ኤስ አስተር ድራገን 50 ሺህ የፊት ማስክ እና 500 የሜዲካል ልብስ 9. ኮካ ኮላ ካምፓኒ 12 ሺህ 672 ፍሬ ፋንታ ለስላሳ መጠጥ ፣ 208 ኩንታል ዱቄት፣355 ካርቶን ዘይት፣401 ፓስታ እና 81 ካርቶን ሳኒታይዘር 10. የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን የዋሊያዎቹ እና የሉሲዎቹ 120 ሺህ ብር 11. የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ፣የፕሪሚየር ሊግ እና ሱፐር ሊግ አሰልጣኞች 125 ሺህ ብር 12. የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አርሶ አደሮች እና ግብርና ኮሚሽን 150 ኩንታል ቦቆሎ እና ለ1655 አባዎራዎች የጽዳት እቃ እና የምግብ ሸቀጥ 13. ሜይላንች ካፌ እና ሬስቶራንት 50 ሺህ ብር 14. የአልታድ መንደር ነዋሪዎች 70 ሺህ ብር የሚገመት ቁሳቁስ 15. ሳሙኤል ካሳሁን ጠቅላላ አስመጪ አንድ ሚሊዮን ብር የሚያወጣ ጂ.አር.ፒ የውሃ ማጠራቀሚያ ታንከር መለገሳቸውን ከከንቲባ ፅሀፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ይጠቁሟል።