የሀገር ውስጥ ዜና

በኢትዮጵያ ተጨማሪ 2 ሰዎች የኮሮናቫይረስ ተገኘባቸው

By Tibebu Kebede

April 12, 2020

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 4፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኢትዮጵያ ሁለት ተጨማሪ ሰዎች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።

ባለፉት 24 ሰዓታት የላቦራቶሪ ምርመራ ከተደረገላቸው 286 ግለሰቦች መካከል ነው ሁለቱ የኮሮናቫይረስ እንደተገኘባቸው የተረጋገጠው ብለዋል የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ።