አዲስ አበባ፣ መጋቢት 5፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በደቡብ ወሎ ዞን አምባሠል እና አልብኮ ወረዳዎች የካቲት 30 ቀን 2015 ዓ.ም በረዶ ቀላቅሎ በጣለ ዝናብ ምክንያት ከ450 ሚሊየን ብር በላይ ግምት ያለው ሰብልና ንብረት ወድሟል፡፡
የደቡብ ወሎ ዞን አደጋ መከላከል እና ምግብ ዋስትና ተጠሪ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ኢብራሂም ይመር እንዳሉት÷ በረዶ ቀላቅሎ የጣለው ዝናብ በእንስሳት፣ በመስኖሰብል፣ በአትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም በመኖሪያ ቤት ላይ ጉዳት አድርሷል፡፡
በዚህም በ571 ሔክታር መሬት ላይ የነበረ ሰብልን ጨምሮ አትክልትና ፍራፍሬ ሙሉ በሙሉ ወድሟል ነው ያሉት፡፡
በተጨማሪም አምስት የቀንድ ከብት፣ 29 በግና ፍየል፣ ሥድስት መኖሪያ ቤት፣ 29 የንብ ቀፎ እንዲሁም 220 ሔክታር የሚያለማ የመስኖ ካናል መውደሙን አብራርተዋል፡፡
ለጉዳቱ የተጋለጡ የህብረተሠብ ክፍሎች አስቸኳይ የዕለት እርዳታ፣ መጠለያ እና አልባሣት እንደሚያስፈልጋቸው ኃላፊው ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ተናግረዋል፡፡
በዮሐንስ ደርበው
#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/ ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!