አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 4፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በሀረማያ ዩኒቨርስቲ በሁለት ሰዓት ልዩነት 384 ናሙና መመርመር የሚችል የኮሮና ቫይረስ መመርመሪያ ላብራቶሪ ማዕከል ተመረቀ።
በሀረማያ ዩኒቨርስቲ ሐረር ካምፓስ ተመርቆ አገልግሎት መስጠት የጀመረው የኮሮና ቫይረስ መመርመሪያ መሣሪያው በተለይ በሐረሪ ክልል እና በአካባቢው በቫይረሱ የተጠረጠሩ ሰዎችን በመመርመር በውጤቱ በአፋጣኝ የመከላከል እርምጃ ለመውሰድ የሚያስችል እንደሆነ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ተናግረዋል።