Fana: At a Speed of Life!

አሜሪካ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ዘመን ተሻጋሪ ግንኙነት ታጠናክራለች- አንቶኒ ብሊንከን

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 6፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን አሜሪካ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ዘመን ተሻጋሪ ግንኙነት እንደምታጠናክር ተናገሩ።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ ያደረጉትን ይፋዊ የስራ ጉብኝት አስመልክቶ ለጋዜጠኞች መግለጫ እየሰጡ ነው።

በመግለጫቸውም÷ በፕሪቶሪያ እና በናይሮቢ የተደረሰው የሰላም ስምምነት ተፈጻሚነት ላይ በሁለቱም ወገን የተጠናከረ ስራ ሊሰራ እንደሚገባ አንስተዋል።

ዘላቂ ሰላም ለማምጣትም የሽግግር ፍትህን አጠናክሮ መተግበር እና ሃገራዊ ምክክር ማከናወን ተገቢ መሆኑን አመላክተዋል፡፡

በለይኩን ዓለም

#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.