ስፓርት

በሶል ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድል ቀናቸው

By Mikias Ayele

March 19, 2023

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 10፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በደቡብ ኮሪያ በተካሄደው የ77ኛው ሶል ማራቶን ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድል ቀንቷቸዋል፡፡

በውድድሩ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከ1ኛ እስከ 3ኛ ያለውን ደረጃ በመያዝ ርቀቱን አጠናቀዋል፡፡

በውድድሩ አትሌት አምደወርቅ ዋለልኝ 2 ሰዓት ከ5 ደቂቃ ከ26 ሴኮንድ በመግባት ቀዳሚ ሲሆን ፥ አትሌት ሺፈራው ታምሩ እና አትሌት ሀፍቱ አሰፋ ሁለተኛ እና ሦስተኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቀዋል፡፡

ባለፈው ዓመት በተካሄደው 76ኛው የሶል የወንዶች ማራቶን ውድድር ኢትዮጵያዊው አትሌት ሞስነት ገረመው አሸናፊ እንደነበር የሚታወስ ነው፡፡