የሲዳማ ክልል ምክር ቤት መደበኛ ጉባዔውን ማካሄድ ጀመረ
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 11፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የሲዳማ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 2ኛ የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባዔውን ማካሄድ ጀምሯል።
በጉባኤው በክልሉ በበጀት ዓመቱ ባለፉት 7 ወራት የተከናወኑ ሥራዎች ሪፖርት ቀርቦ ወይይት ይደረግበታል።
እንዲሁም የተለያዩ አዋጆች እና ሹመቶች ለምክር ቤቱ ቀርበው እንደሚፀድቁም ይጠበቃል፡፡
ጉባኤው ለሁለት ቀናት እንደሚካሄድ ታውቋል፡፡
በቢቂላ ቱፋና ታመነ አረጋ