Fana: At a Speed of Life!

የዓለም ጤና ድርጅት 35 ሜትሪክ ቶን የድንገተኛ አደጋ የሕክምና ቁሳቁስ ለትግራይ ክልል እያከፋፈለ ነው

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 11፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የዓለም ጤና ድርጅት የድንገተኛ አደጋ የሕክምና መሥጫ ቁሳቁስ በትግራይ ክልል ለሚገኙ ጤና ተቋማት እያቀረበ መሆኑን አስታወቀ፡፡

ድርጅቱ አቅርቦቱን የላከው ከአውሮፓ ኅብረት ሲቪል ጥበቃ እና የሰብአዊ ዕርዳታ፣ ከአሜሪካ ተራድዖ ድርጅት እንዲሁም ከተመድ የድንገተኛ አደጋ ፈንድ ጋር በመተባበር ነው፡፡

35 ሜትሪክ ቶን የሕክምና መሥጫ ቁሳቁሱ በትግራይ ክልል እየተከፋፈለ መሆኑንም ከገጹ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

አቅርቦቱ በክልሉ የሕክምና ዕርዳታ ለሚያስፈልጋቸው 700 ሺህ ያኅል ሰዎች የሚውል ሲሆን፥ በክልሉ ማዕከላዊ እና ሰሜን ምዕራብ ዞኖች ለሚገኙ 48 የጤና ተቋማት እየተከፋፈለ እንደሚገኝ ተገልጿል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.