የሀገር ውስጥ ዜና

የኔ ያልነውን የጋራ ሀብት በማድረግና በማልማት አብረን ሠርተን እንበልጽግ – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ

By ዮሐንስ ደርበው

March 20, 2023

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 11 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የኔ ያልነውን የጋራ ሀብት በማድረግና በማልማት አብረን ተግተን ሠርተን እንበልጽግ ሲሉ መልዕክት አስተላለፉ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት ምርጥ ሀገር እንዳለን ጠቅሰዋል።

በመልዕክታቸውም “ዓይናችንን ገልጠን ብንሠራ ለዓለም መስሕብ መሆን የሚችሉ በርካታ ቦታዎች በሀገራችን አሉ” ብለዋል።

አካባቢን መቃኘትና መፈተሽ እንደሚገባም በመልዕክታቸው ጠቅሰዋል።

“የኔ ያልነውን የጋራ ሀብት እናድርግ፤ እናልማ፤ አብረን ተግተን ሠርተን እንበልጽግ ሲሉም መልዕክት አስተላልፈዋል።

#Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/ ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!