ዶ/ር ግርማ አመንቴ በኢትዮጵያ ከጀርመን አምባሳደር ጋር ተወያዩ
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 15፣ 2015(ኤፍ ቢ ሲ) የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ በኢትዮጵያ ከጀርመን አምባሳደር ስቴፈን ኡር ጋር ተወያይተዋል፡፡
በውይይታቸውም÷ ኢትዮጵያ እና ጀርመን ባላቸው የረጅም ጊዜ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ዙሪያ መምከራቸውን የኤምባሲው መረጃ ያመላክታል፡፡
ከዚህ ባለፈም በግብርናው ዘርፍ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ማጠናከር በሚችሉበት ሁኔታ ላይ መወያየታቸው ተገልጿል፡፡