አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 6፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ በኮሮና ቫይረሰ የተቋረጠወን ትምህርት በቴሌቪዥን ለማስጀመር ዝግጅት ማጠናቀቁን ገለፀ።
የከተማ አስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ የቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ አዲሱ ሻንቆ ለፋና ብሮድ ካስቲንግ ኮርፖሬት እንደተናገሩ፥ የቴሌቪዥን ትምህርት የሙከራ ስርጭት ሚያዚያ 7 2012 ዓ.ም በአፍሪ ሄልዝ የቴሌቪዥን የሚጀምር መሆኑን ገልፀዋል።