የሀገር ውስጥ ዜና

ኮቪድ19ን የመከላከል ሥራው በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ መሆኑን ዐውቄያለሁ- ጠ/ሚ ዐቢይ

By Tibebu Kebede

April 14, 2020

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 6፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የኮሮናቫይረስ ኮቪድ19ን ለመከላከል ከተቋቋመው የሚኒስቴሮች ኮሚቴ ጋር ተወያዩ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ በፌስቡክ ገፃቸው እንዳስታወቁት፥ “ኮቪድ19ን ለመከላከል ከተቋቋመው የሚኒስቴሮች ኮሚቴ ባደረክሁት ውይይት ቫይረሱን የመከላከል ሥራው በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ መሆኑን ዐውቄያለሁ” ብለዋል።