ሚኒስቴሩ በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች ያሰባሰበውን ድጋፍ አስረከበ
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 20፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር በኦሮሚያ ክልል በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች ያሰባሰበውን 8 ሚሊየን 45 ሺህ ብር ለክልሉ መንግሥት አስረከበ፡፡
ሚኒስቴሩ በኦሮሚያ ክልል ቦረና፣ ባሌ፣ ጉጂ፣ አርሲ እና ሐረርጌ አካባቢዎች ያጋጠመውን የድርቅ አደጋ ለመመከት እንዲቻል የንግዱን ማህበረሰብ በማስተባበር ያሰባሰበውን ገንዘብ ነው ዛሬ ያስረከበው፡፡
የኦሮሚያ ክልል መንግስትም ለተደረገው ድጋፍ የምስጋና የምስክር ወረቀት ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አበርክቷል፡፡
#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!