Fana: At a Speed of Life!

ሚኒስቴሩ በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች ያሰባሰበውን ድጋፍ አስረከበ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 20፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር በኦሮሚያ ክልል በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች ያሰባሰበውን 8 ሚሊየን 45 ሺህ ብር ለክልሉ መንግሥት አስረከበ፡፡

ሚኒስቴሩ በኦሮሚያ ክልል ቦረና፣ ባሌ፣ ጉጂ፣ አርሲ እና ሐረርጌ አካባቢዎች ያጋጠመውን የድርቅ አደጋ ለመመከት እንዲቻል የንግዱን ማህበረሰብ በማስተባበር ያሰባሰበውን ገንዘብ ነው ዛሬ ያስረከበው፡፡

የኦሮሚያ ክልል መንግስትም ለተደረገው ድጋፍ የምስጋና የምስክር ወረቀት ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አበርክቷል፡፡

#Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.