Fana: At a Speed of Life!

የሀረሪ ክልል መስተዳድር ካቢኔ ውሳኔ አሳለፈ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 21፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ)የሀረሪ ክልል መስተዳድር ካቢኔ በተለያዩ ረቂቅ ደንቦችና አዋጆች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ።

ካቢኔው በዛሬው እለት ባካሄደው አስቸኳይ ውይይት ነው በተለያዩ ረቂቅ ደንቦችና አዋጆች ላይ ውሳኔ ያሳለፈው፡፡

ካቢኔው ተወያይቶ ውሳኔ ያሳለፈው በጠቅላይ አቃቤ ህግያን መተዳደሪያ ደንብና ማረሚያ ቤት ማቋቋሚያ ረቂቅ አዋጅ ላይ ነው።

በዚህም መስተዳድር ምክር ቤቱ በጠቅላይ አቃቤ ህግያን መተዳደሪያ ደንብ በሙሉ ያፀደቀ ሲሆን÷ ማረሚያ ቤት ማቋቋሚያ ረቂቅ አዋጅን ደግሞ ለክልሉ ምክር ቤት መምራቱን ከክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.