ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶ/ር) ከአውሮፓ ሕብረት የፓርላማ አባላት ጋር ተወያዩ
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 21፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶ/ር) ከአውሮፓ ሕብረት የፓርላማ አባላት ጋር ተወያይተዋል፡፡
በርዕሰ መስተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶ/ር) የተመራ የልዑካን ቡድን ለስራ ጉብኝት ቤልጂዬም ብራስልስ ገብቷል፡፡
ልዑካኑ በብራስልስ ቆይታው ከአውሮፓ ሕብረት የፓርላማ አባላት ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ መክረዋል፡፡