የሀገር ውስጥ ዜና

ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ዘውዴ በመኖሪያ ቤታቸው የአፍጥር ዝግጅት አካሄዱ

By Feven Bishaw

March 31, 2023

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 22፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የረመዳን ጾምን ምክንያት በማድረግ ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ዘውዴ በመኖሪያ ቤታቸው የአፍጥር ዝግጅት አካሂደዋል፡፡

በሥነ ስርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሼክ ሃጂ ኢብራሂም፣ የምክር ቤቱ አባላትና የእምነቱ አባቶች ተገኝተዋል፡፡

ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ባለፈው ዓመትም በመኖሪያ ቤታቸው የአፍጥር ዝግጅት ማካሄዳቸው ይታወሳል፡፡