Fana: At a Speed of Life!

በሕገ-ወጥ መንገድ የተገጠሙ ቆጣሪዎች ተያዙ

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 22 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ ገርጂ ጎሮ አካባቢ ልዩ ስሙ አሳማ እርባታ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ 17 ቆጣሪዎች በሕገ-ወጥ መንገድ ተገጥመው መገኘታቸውን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታወቀ።

በሕገ-ወጥ መንገድ ተገጥመው የተገኙት ቆጣሪዎች ከእነፍጆታቸው አጠቃላይ ግምት ከ343 ሺህ ብር በላይ መሆኑን አገልግሎቱ ገልጿል።

የምሥራቅ አዲስ አበባ ዲስትሪክት ሕግ ክፍል ከፖሊስ ጋር በመተባበር በሕገ-ወጥ መንገድ የተገጠሙት ቆጣሪዎች፣ ኬብል እና ምሰሶ ተነሥተው ወደ ተቋሙ ገቢ እንዲሆኑ ማድረጉን አስታውቋል።

የአካባቢው ፖሊስ በሕገ-ወጥ ተግባሩ ላይ ምርመራ እያከናወነ እንደሚገኝ የአገልግሎቱ መረጃ ያመለክታል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.