Fana: At a Speed of Life!

“መጋቢት 24 የመንግስትን ስርዓት በሴራና ሃይል የመቀየር አስተሳሰብን የዘጋ ታሪካዊ ቀን ነው” – የአምቦ ከተማ ነዋሪዎች

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 24፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን በአምቦና ሌሎች ከተሞች ከለውጡ በኋላ የተገኘውን ድልና ስኬት ለማስቀጠል ያለመ የድጋፍ ሰልፍ ተካሄደ፡፡

የድጋፍ ሰልፉ ተሳታፊዎች ከመጋቢት 24 ቀን 2010 ዓ.ም ወዲህ በክልሉ የተመዘገቡ ድልና ስኬቶችን የሚያንጸባርቁ መልዕክቶችን አስተላልፈዋል፡፡

በድጋፍ ሰልፉ “መጋቢት 24 የመንግስትን ስርዓት በሴራና በሃይል የመቀየር አስተሳሰብን የዘጋ ታሪካዊ ቀን ነው፣ ሌብነትና ስንፍና የመጋቢት 24 ጠላቶች ናቸው የሚሉና ሌሎች መፈክሮች ተደምጠዋል፡፡

በድጋፍ ሰልፉ በርካታ ቁጥር ያላቸው የከተማዋ እና አካባቢው ነዋሪዎች ተሳትፈዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.