ዓለምአቀፋዊ ዜና

ትራምፕ አሜሪካ ለዓለም ጤና ድርጅት የምታደርገውን የገንዘብ ድጋፍ እንድታቋርጥ ውሳኔ አሳለፉ

By Tibebu Kebede

April 15, 2020

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 7፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ዋሽንግተን ለዓለም ጤና ድርጅት የምታደርገውን የገንዘብ ድጋፍ እንድታቋርጥ ትዕዛዝ ማስተላለፋቸውን አስታወቁ።

ፕሬዚዳንቱ የዓለም ጤና ድርጅት ከኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ጋር ተያይዞ ሃላፊነቱን አልተወጣም ሲሉ ወቅሰዋል።