አትሌት አበጀ አያና የፓሪስ ማራቶንን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 24፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) አትሌት አበጀ አያና ዛሬ የተካሄደውን የፓሪስ ማራቶን አሸነፈ፡፡
አትሌት አበጀ ውድድሩን ያሸነፈው 2 ሰዓት ከ7 ደቂቃ ከ14 ሰከንድ በሆነ ጊዜ በመግባት ነው።
ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት ጉዬ አዶላ 2 ሰዓት 7 ደቂቃ ከ35 ሰከንድ በመግባት ሁለተኛ ሆኖ ውድድሩን መጨረሱን ሬውተርስ ዘግቧል፡፡
እንዲሁም ኬንያዊው አትሌት ጆስፋት ቦይት ሦስተኛ ደረጃን ይዞ ውድድሩን አጠናቋል፡፡
#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!