Fana: At a Speed of Life!

የቀድሞ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ፍርድ ቤት ቀረቡ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 26፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የቀድሞ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በዛሬው ዕለት በኒውዮርክ ፍርድ ቤት ቀርበዋል፡፡

በአሜሪካ ታሪክ በወንጀል የተከሰሱ የመጀመሪያው የቀድሞ ፕሬዚዳንት የሆኑት ዶናልድ ትራምፕ÷በአሁኑ ስዓትም የቀረበባቸው ክስ ለመስማት ኒዮርክ በሚገኘው ፍርድቤት ተገኝተዋል፡፡

ዶናልድ ትራምፕ ከወሲብ ፊልም ተዋናይት ስቶርሚ ዳንኤልስን ጋር የፈጸሙት ጾታዊ ግንኙነት ይፋ እንዳይሆን ዝም ለማሰኘት 130 ሺህ ዶላር ከፍለዋል በሚል ነው ለክስ የተዳረጉት፡፡

ትራምፕ በፈረንጆቹ 2016 በአሜሪካ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ አሸናፊ ከመሆናቸው ቀደም ብሎ ለግለሰቧ የከፈሉት ገንዘብ አለ በሚል በኒውዮርክ ጠበቆች ምርመራ ሲደረግ መቆየቱ ተጠቁሟል፡፡

ምርመራው ትራምፕ ከቀድሞዋ የወሲብ ፊልም ተዋናይት ጋር የፈጸሙት ጾታዊ ግንኙነት ይፋ እንዳይሆን ገንዘብ ከፍለዋል በሚል ሲካሄድ መቆየቱን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡

#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.