Fana: At a Speed of Life!

ጣሊያን ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ሁለንተናዊ ግንኙነት ለማሳደግ ቁርጠኛ መሆኗን ገለጸች

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 26፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን በኢትዮጵያ ከጣሊያን አምባሳደር አጎስቲኖ ፓሌሴ ጋር ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸውም÷ ኢትዮጵያ እና ጣሊያን ያላቸውን የሁለትዮሽ እና ዘርፈ ብዙ ግንኙነት ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መክረዋል፡፡

አምባሳደር አጎስቲኖ ፓሌሴ ÷ ኢትዮጵያ ለቀጣናው ሰላም እና መረጋጋት ወሳኝ ሚና ያላት ሀገር መሆኗን አንስተዋል፡፡

የጣሊያን መንግስት ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን ሁለንተናዊ ግንኙነት ይበልጥ ለማሳደግ ቁርጠኛ እንደሆነ ማረጋገጣቸውንም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.