Fana: At a Speed of Life!

በጅማ ከተማ የጎዳና ላይ የኢፍጣር ሥነ-ሥርዓት ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 28፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በጅማ ከተማ ለ2 ሺህ ሰዎች የጎዳና ላይ የኢፍጣር ሥነ-ስርዓት ተካሂዷል፡፡

ስነስርዓቱ በቀርጫሼ ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር እንዲሁም በጅማ ከተማና ዞን አስተዳደር የተዘጋጀ ነው፡፡

በአፍጥር ስነ-ስርዓቱ የከተማው አቅመ ደካሞችን ጨምሮ በተለያዩ ደረጃ ያሉ የከተማዋ ነዋሪዎች ተገኝተዋል።

የሰቃ ወረዳ ኢማም ሼህ ወዚር መሃመድ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት÷ የረመዳን ወር ያላቸው ለሌላቸው የሚያካፍሉበት የተቀደሰ ወር ነው፡፡

በመሆኑም በተቀሩት የፆም ቀናት የእስልምና እምነት ተከታዮች በዘር በሃይማኖት ሳይለዩ አቅመ ደካሞች በመርዳት እንድያሳልፉ መልክት አስተላልፈዋል።

በሙክታር ጣሓ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.