Fana: At a Speed of Life!

በስሎቬኒያ የውጭና የአውሮፓ ጉዳዮች ሚኒስትር የተመራ ልዑክ ለስራ ጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ ይመጣል

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 29 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በስሎቬኒያ የውጭና የአውሮፓ ጉዳዮች ሚኒስትር ታኒያ ፋየን የተመራ ልዑክ በኢትዮጵያ የሦስት ቀናት ይፋዊ የሥራ ጉብኝት እንደሚያደርግ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡

የኢፌዴሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ እንደሚያመላክተው ሚኒስትሯ ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡት ከከፍተኛ የልዑካን ቡድናቸው ጋር ነው፡፡

በኢትዮጵያ የሚኖራቸው የሥራ ቆይታም ከፊታችን ሚያዚያ 3 እስከ 5 ቀን 2015 ዓ.ም መሆኑ ተመላክቷል፡፡

ልዑካኑ በቆይታቸውም ከኢትዮጵያ መንግስት የተለያዩ ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች ጋር ይመክራሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

 

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.