Fana: At a Speed of Life!

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከስሎቬኒያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ታንያ ፋዬን ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 4፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከስሎቬንያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ታንያ ፋዬን ጋር ተወያዩ።

በዚህም ወቅት፥ በኢትዮጵያና በስሎቬኒያ የሁለትዮሽ ግንኙነት ላይ ውጤታማ ውይይት ማድረጋቸውን ነው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው በኩል ያስታወቁት።

በስሎቬኒያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ታንያ ፋዬን የተመራው የሀገሪቱ ልዑክ በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ለማድረግ ከቀናት በፊት ነበር ወደ አዲስ አበባ የመጣው።

በቆይታውም የተለያዩ የመንግስት የስራ ሀላፊዎችን በማግኘት በሁለቱ ሀገራት ግንኙነት ዙሪያ መክሯል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.