የሀገር ውስጥ ዜና

ከ60 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገዙ ትራክተሮች ለዞኖች ተሰጡ

By Shambel Mihret

April 12, 2023

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 4፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል 22 ትራክተሮችን ለዞኖች አስረከበ፡፡

ግብርናውን ለማዘመን የክልሉ መንግስት ከ60 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ 22 ትራክተሮችን ገዝቶ ለዞኖች ማስረከቡን የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር ኢ/ር) በርክክቡ ወቅት ተናግረዋል፡፡

ትራክተሮቹ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ከፍተኛ ፋይዳ እንዳላቸው መገለጹን የክልሉ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡