የሀገር ውስጥ ዜና

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ለጣልያን ጠቅላይ ሚንስትር የእራት ግብዣ አደረጉ

By Tamrat Bishaw

April 14, 2023

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 6፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለጣልያን ጠቅላይ ሚንስትር ጆርጂያ ሜሎኒ በታላቁ ቤተ መንግስት የክብር የእራት ግብዣ አደረጉ።

በታላቁ ቤተ መንግስት በተደረገው የክብር እራት ግብዣ ጠቅላይ ሚኒስትሮቹ የሁለትዮሽ ውይይት ማድረጋቸውን ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።