አይሻ መሀመድ (ኢ/ር) ከፋኦ የኢትዮጵያ ተጠሪ ጋር ተወያዩ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 10፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አይሻ መሀመድ(ኢ/ር) ከተባባሩት መንግስታት ድርጅት የምግብና እርሻ ድርጅት የኢትዮጵያ ተጠሪ ፋራይ ዚሙድዚ ጋር ተወያይተዋል፡፡
በውይይታቸው በጋራ መስራት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ መክረዋል፡፡
ሚኒስቴሩ አዲስ ከመቋቋሙ ጋር ተያይዞ ያሉ ክፍተቶችን በመለየት በተለይም በመስኖ ስታንዳርዶችና ኮዶችን በማዘጋጀት ዙሪያ በትብብር ለመስራትም መስማማታቸውን ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡