Fana: At a Speed of Life!

በምስራቅ ኢትዮጵያ ተቋርጦ የነበረው የኤሌክትሪክ ሃይል መስተካከሉ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 12፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ላይ በተፈፀመ ስርቆት ኃይል የተቋረጠበት የምስራቅ ኢትዮጵያ አካባቢ በአማራጭ መስመር ኃይል አግኝቷል።

ኃይል የተቋረጠባቸው አካባቢዎች ከቆቃ በአማራጭ ኃይል እንዲያገኙ ለማድረግ የተደረገው ጥረት ውጤት በማስገኘቱ የምስራቅ ኢትዮጵያ ከተሞችና ጅቡቲ ኃይል ማግኘት ችለዋል።

ከአዋሽ ወደ ድሬዳዋ በተዘረጋው የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ላይ ሁርሶ አካባቢ በተፈፀመ ስርቆት ምሽቱን በምስራቅ ኢትዮጵያ ትልልቅ ከተሞችና አካባቢያቸው ሙሉ በሙሉ ኃይል ተቋርጦ እንደነበር ይታወሳል፡፡ም ብለዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.