Fana: At a Speed of Life!

ከሰላም ስምምነቱ ጋር በተያያዘ በኢትዮጵያ የተከናወነው ሌሎችን ያስተምራል – ኡሁሩ ኬንያታ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 15፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢፌዲሪ መንግሥት እና ህወሓት ያደረጉት የሰላም ስምምነት ለሌሎች አፍሪካውያን ማሳያ ነው ሲሉ የኬንያ የቀድሞ ፕሬዚዳንት እና በስምምነቱ ከፍተኛ ሚና የነበራቸው ኡሁሩ ኬንያታ ተናገሩ፡፡

በወዳጅነት አደባባይ እየተካሔደ በሚገኘው ‘ጦርነት ይብቃ፤ ሰላም እናጽና’ የምስጋና እና የዕውቅና ሥነ ስርዓት ላይ ባደረጉት ንግግር÷ ይህ ቀን የኢትዮጵያውያን የሰላም ቀን ነው ብለዋል፡፡

እረጅሙ የሰላም ማስፈን ሂደት በስኬት ተጠናቆ ለዚህ መብቃት በመቻሉ በሂደቱ ተሳታፊ የነበራችሁ ሁሉ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

በኢትዮጵያ የሆነው ለተቀረው የአፍሪካ ሀገራት ትልቅ ማሳያ ነው ያሉት ኡሁሩ÷ አፍሪካ ለዘላቂ ሰላሟ እንደትሠራ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

#Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.