በሉሜ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ10 ሰዎች ሕይወት አለፈ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 18፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን ሉሜ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ10 ሰዎች ሕይወት አለፈ፡፡
የሉሜ ወረዳ የትራፊክ ደህንነት አስተባባሪ ኢንስፔክተር ተክልየ ታምሩ እንደገለጹት÷አደጋው ዛሬ ጠዋት ከአረርቲ ከተማ ወደ አዳማ ከተማ ሲጓዝ የነበረ ተሽከርካሪ ከቆመ መኪና ጋር በመጋጨቱ ነው የተከሰተው፡፡
በአደጋው 10 ሰዎች ለህልፈት መዳረጋቸውን የገለጹት ኢንስፔክተሩ÷ በአከባቢው ከዚህ በፊት መሰል አደጋዎች መከሰታቸውን ጠቁመዋል፡፡
የአደጋው መንስኤ ከፍጥነት በላይ ማሽከርከር እንደሆነ መገለጹንም ከሉሜ ወረዳ ኮሙኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡