Fana: At a Speed of Life!

ወ/ሮ ሙፈሪሃት ከጀርመኑ ዓለም አቀፍ ድርጅት የሥራ ኃላፊዎች ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 18፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የሥራና ክህሎት ሚንስትር ሙፈሪሃት ካሚል ከጀርመኑ ዓለም አቀፍ ድርጅት (ኬ ኤፍ ደብሊው)የሥራ ኃላፊዎች ጋር ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸውም ÷ በድርጅቱ ድጋፍና የቅርብ ትትል የተከናወኑ ተግባራት እና የተደረጉ ድጋፎች ውጤታማ መሆናቸው ተገልጿል፡፡

በቀጣይ በድርጅቱ በኩል ተጨማሪ ድጋፍ በሚደረግበትና ግንኙነቱ ተጠናክሮ በሚቀጥልበት ሁኔታ ላይ መምከራቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመላክታል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.