Fana: At a Speed of Life!

ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በግርማ የሺጥላ ግድያ የተሰማቸውን ሀዘን ገለጸ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 19፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ግርማ የሺጥላ ግድያ የተሰማቸውን ሃዘን ገለጹ፡፡

ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ ፥ “በወንድሜ በአቶ ግርማ የሺጥላ ድንገተኛ ሞት የተሰማኝ ሐዘን በጣም ጥልቅ ነው” ብለዋል፡፡

አቶ ግርማ በሃሳብ ልዕልና የሚያምኑ፣ ለሀገራዊ አንድነትና ለሕዝቦች ወንድማማችነት የሚታገሉ ኢትዮጵያዊ እንደነበሩም አውስተዋል፡፡

ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ÷ ለሥራ ባልደርቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸውና ለቤተሰቦቻቸው መጽናናትን ተመኝተዋል፡፡

በተመሳሳይ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በግርማ የሺጥላ ግድያ የተሰማውን ሀዘን ገልጿል፡፡

በመግለጫውም ፥ ጽንፈኞች በፈጸሙት አስነዋሪ ተግባር የአማራ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊና የብልፅግና ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል የሆኑት ወንድም ግርማ የሺጥላ ህይወታቸው ማለፉን ሲንሰማ ከፍተኛ ሀዘን ተሰምቶናል ብለዋል ::

ጽንፈኝነት ለማንም የማይጠቅም የዘመናችን በሽታና የአንድነታችን ነቀርሳ ነው ያለው ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ፥ ሁላችንም አጥብቀን ልንታገለውና ልንኮንነው ይገባል ብሏል።

አቶ ግርማ የሺጥላ ለአማራ ክልል እንዲሁም ለሀገራቸው ህዝቦች ልማትና እድገት ደከመኝ ታከተኝ ሳይሉ ሲለፉና ሲታክቱ የነበሩ ታማኝ የህዝብ ልጅ እንደነበሩም አንስቷል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.