የሀገር ውስጥ ዜና

ኤጀንሲው በጃክ ማ የተበረከቱ የህክምና ቁሳቁሶች እያሰራጨ መሆኑን ገለፀ

By Tibebu Kebede

April 21, 2020

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 13፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ መድሐኒት አቅራቢ ኤጀንሲ በመጀመሪያ ዙር በጃክ ማ የተበረከቱትን የኮሮናቫይረስ (ኮቪድ-19) መመርመሪያ መሳሪያዎችና የህክምና መገልገያዎችን እያሰራጨ መሆኑን አስታወቀ።

በጃክ ማ ሁለተኛ ዙር የተሰጠው ድጋፍም ለስርጭት ዝግጁ ሆኗል ተብሏል።