የሀገር ውስጥ ዜና

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ከፊንላንድ አቻቸው ፔካ ሃቪስቶ ጋር በስልክ ተወያዩ

By Tibebu Kebede

April 21, 2020

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 13፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ከፊንላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፔካ ሃቪስቶ ጋር በሁለትዮሽ፣ ክልለዊ እና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ዙሪያ የስልክ ውይይት አድርገዋል።

አቶ ገዱ በነበራቸው የስልክ ውይይት ኢትዮጵያ እና ፊንላንድ ዘመናትን ያስቆጠረ ግንኙነት እንዳላቸው አስታውሰው ሁለቱ አገራት ያላቸውን ግንኙነት ለማጠናከር ኢትዮጵያ ቁርጠኛ መሆኗን መግለፃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽህፈት ቤት መረጃ ያመለክታል።