Fana: At a Speed of Life!

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄና ውጤቶች የፓናል ውይይት እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 29፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄና ውጤቶች የፓናል ውይይት መድረክ በሚሊኒየም አዳራሽ እየተካሄደ ነው።

በውይይቱ ላይ የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሺዴ፣ የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል፣ የፕላንና ልማት ሚኒስትሯ ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር )፣ የጉምሩክ ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል።

ከተጀመረ አንድ ዓመቱን ያስቆጠረው ኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በማምረቻው ዘርፍ በርካታ ውጤቶችን አስገኝቷል ተብሏል፡፡

አቶ መላኩ አለበል በዚሁ ወቅት÷ የማምረቻው ዘርፍ ቀጣይነት ያለው እና ውድድር የበዛበት ዘርፍ ነው ብለዋል፡፡

በተለይም የኮሮና ቫይረስ መምጣት እና የጸጥታ ሁኔታውም ዘርፉን ይበልጥ ፈተና ላይ እንዲወድቅ እንዳደረገውም አንስተዋል ።

በዚህም የኢንዱስትሪዎች የማምረት አቅም እንዲወርድ እና ኢንቨስትመንት እንዲቀዛቀዝ ማድረጉንም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የተጀመረውም ቀደም ሲል ስንከተለው ከነበረው ነባራዊ ሁኔታ በመውጣት ና ችግሩን ለመቋቋም ያለመ ነው ብለዋል ።

በተጨማሪም በዘርፉ የነበሩ ማነቆዎችን በመለየት የተለየ መንገድ እንድንከተል የሚያስገድድ ነው ሲሉ ገልጸዋል፡፡

በዚህ ዘርፍ በ10 ዓመቱ ዕቅድ ውስጥ ለ5 ሚሊየን ዜጎች የስራ ዕድል ለመፍጠር መታቀዱም ተጠቁሟል፡፡

በመሳፍንት እያዩ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.