ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከማልታ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 30፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከማልታ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኢያን ቦርግን ጋር ተወያዩ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሁፍ÷የማልታ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኢያን ቦርግን ዛሬ አግኝቻቸዋለሁ ብለዋል።
በንግድ እና በኢንቨስትመንት ግንኙነት ላይ፣ በተለይም የቱሪዝም ዘርፍን ለማሳደግ በተጠናከረ መልኩ ከማልታ ጋር ስለምንሠራበት ሁኔታ ተወያይተናልም ነው ያሉት።