Fana: At a Speed of Life!

ብሔራዊ ባንክ፥ለሳፋሪኮም የሞባይል የገንዘብ ክፍያ አገልግሎት ፈቃድ ሰጠ

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 3 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ብሔራዊ ባንክ፥ ሳፋሪኮም የሞባይል የገንዘብ ክፍያ አገልግሎት እንዲጀምር የሚያስችለውን ፈቃድ ሰጠ፡፡

የብሔራዊ ባንክ ገዥ አቶ ማሞ ምህረቱ እንዳስታወቁት÷ ባንኩ የዲጅታል ፋይናንስ አገልግሎት መስጠት የሚያስችለው የሞባይል የገንዘብ ክፍያ አገልግሎት ፈቃድ ለሳፋሪኮም ሰጥቷል፡፡

ይህም ሳፋሪኮም በኢትዮጵያ የሞባይል የገንዘብ ክፍያ አገልግሎት ፈቃድ ያገኘ የመጀመሪያው የውጭ ሀገር ኩባንያ ያደርገዋል ብለዋል፡፡

ባንኩ በጥሬ ገንዘብ የሚደረግን ግብይት በዲጂታል ክፍያ ስርዓት ለመተካት የሚደረገውን ጥረት እንደሚደግፍም አረጋግጠዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.