Fana: At a Speed of Life!

በመዲናዋ ሲሚንቶ ከታሪፍ በላይ ሲሸጡ የተገኙ 89 የንግድ ሱቆች ላይ እርምጃ ተወሰደ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 3፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) መንግስት ያወጣውን የሲሚንቶ መሸጫ ዋጋ በመተላለፍ ከታሪፍ በላይ ሲሸጡ የተገኙ 89 የንግድ ሱቆች ላይ እርምጃ መውሰድ የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ አስታወቀ፡፡

ቢሮው መንግሥት ያወጣው የሲሚንቶ ማከፋፈያና የችርቻሮ ተመን ዋጋ እንዲከበር ተደጋጋሚ ውይይት ማድረጉን አስታውሷል፡፡

ይሁን እንጂ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከተማና በለሚኩራ ክ/ከተማ ከተተመነው የሲሚንቶ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በላይ በመሸጥና ምርት በመደበቅ 58 ሱቆች ላይ እርምጃ መውሰዱን ገልጿል፡፡

በተመሳሳይ ከታሪፍ በላይ በመሸጥ 10 ሱቆች እና ምርት በማሸሽ 21 የመሸጫ ሱቆች ላይ እርምጃ መውሰድ መቻሉን የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ መረጃ ያመላክታል፡፡

ቢሮው የተጀመረውን አሰራር የማስጠበቅ ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ነው ያስታወቀው፡፡ላይ ንግግር  ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.