የሀገር ውስጥ ዜና

“ኦሬንጅ”በቴሌኮሙ ዘርፍ በኢትዮጵያ ለመሰማራት ፍላጎት እንዳለው አስታወቀ

By Meseret Awoke

May 11, 2023

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 3፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) “ኦሬንጅ” የቴሌኮሙኒኬሽን አገልግሎት አቅራቢ በዘርፉ በኢትዮጵያ የመሠማራት ፍላጎት እንዳለው አስታወቀ፡፡

የኢፌዴሪ ገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) በመካከለኛው ምሥራቅ እና በአፍሪካ በቴሌኮም ዘርፍ ላይ የተሠማራውን የ“ኦሬንጅ” ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አሥፈፃሚ ጀሮም ሄኒክ በቢሯቸው ተቀብለው አነጋግረዋል፡፡

ሚኒስትር ዴኤታው ÷ በኢትዮጵያ በቴሌኮሙኒኬሽኑ ዘርፍ ያለውን የኢንቨስትመንት አማራጮች ገልጸውላቸዋል፡፡

የኢፌዴሪ መንግስት ባለፉት ሁለት ዓመታት ለዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እና በቴሌኮሙ ዘርፍ ከውጭ ባለሐብቶች ጋር ለመሥራት ያሳየውን ቁርጠኝነትም አንስተው ፤ በጋራ ሊሠሩባቸው በሚችሉባቸው ሁኔታዎች ላይ መክረዋል፡፡

ለአብነትም ፥ የሳፋሪኮም ኢትዮጵያን በኢትዮጵያ ሥራ መጀመር እና የኢትዮ ቴሌኮምን ትራንስፎርሜሽን ማንሳታቸውን ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

የኦሬንጅ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ጀሮም ሄኒክ በበኩላቸው ፥ ኮርፖሬሽኑ በአፍሪካ የቴሌኮም ገበያ ውስጥ መዋዕለ-ንዋዩን አፍስሶ ያስመዘገበው ስኬት አብራርተዋል።

በቀጣይም “ኦሬንጅ” በዘርፉ ሥራዎቹን ዕውን ለማድረግ በሚችልባቸው ቴክኒካል ጉዳዮች ላይ ለመወያየት ጊዜ ቀጥሯል፡፡

#Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/ ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን