የሀገር ውስጥ ዜና

በኮቪድ 19 ስጋት አንዳንድ የጤና ተቋማት መደበኛ የህክምና አገልግሎት እየሰጡ እንዳልሆነ የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ

By Tibebu Kebede

April 23, 2020

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 15፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኮሮናቫይረስ (ኮቪድ 19) ስጋት አንዳንድ የጤና ተቋማት መደበኛ የህክምና አገልግሎት እየሰጡ እንዳልሆነ የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።

በዚህም ሳቢያ እናቶች በቤት ውስጥ እንዲወልዱ ሆኗል፤ በህክምና ሊድኑ በሚችሉ በሽታዎች የሰው ህይወት እያለፈ እንደሚገኝም ሚኒስቴሩ ገልጿል።