Fana: At a Speed of Life!

በአትላንታ ከተማ ከንቲባ የተመራ ልዑክ  የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጎበኘ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 7፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በአትላንታ ከተማ ከንቲባ አንድሬ ዲከንስ የተመራ የልዑካን ቡድን የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጎብኝቷል፡፡

የልዑካን ቡድኑ አባላት የአየር መንገዱን የስራ እንቅስቃሴና  ዘመናዊ ክፍሎችን ተዘዋውረው መመልከታቸውን የአየር መንገዱ መረጃ ያመላክታል፡፡

ልዑኩ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን  ጣሰው እና ሌሎች  ከፍተኛ  አመራሮች  ጋር  በተለያዩ ጉዳዮች ላይ መወያየቱም ተጠቁሟል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.