Fana: At a Speed of Life!

በሴቶች 10 ሺህ ከ30 ደቂቃ በታች በማጠናቀቅ ኢትዮጵያ ታሪክ ሰራች

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 13፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ሚዛን ዓለም የ10 ሺህ ሜትር የሩጫ ውድድር በአሸናፊነት አጠናቃለች፡፡

አትሌቷ በለንደን ’’ኮንቲነንታል ቱር’’ ላይ በተደረገው የ10 ሺህ ሜትር የሩጫ ውድድር ከ30 ደቂቃ በታች በመግባት በታሪክ 12ኛዋ እንስት ሆናለች፡፡

በዚህ ውድድር ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ሚዛን ዓለም 29 ደቂቃ 58 ሰከንድ 70ማይክሮ ሰከንድ በሆነ ውጤት ነው ውድድሯን ያጠናቀቀችው፡፡

ይህም ታሪክ የማይረሳው የኢትዮጵያ ድል ነው ሲሉ የዓለም አትሌቲክስ እና ሌሎች መገናኛ ብዙሃን አሞካሽተውታል፡፡

#Ethiopia #athletics #victory

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.