ለዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር 6 ነጥብ 5 ቢሊየን ችግኝ እየተዘጋጀ ነው – ጠ/ሚ ዐቢይ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 15፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ለአምስተኛው ዓመት የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር 6 ነጥብ 5 በሊየን ችግኝ እየተዘጋጀ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ገለጹ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ÷”በ5ኛው ዓመት የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ላይ ዘንድሮ በጋራ ለምንተክለው 6 ነጥብ 5 ቢሊየን ችግኝ ዝግጅት በመካሄድ ላይ ነው” ብለዋል።
የፍራፍሬ ዛፎችን በብዛት እንተክላለን ሲሉም አስገንዝበዋል፡፡